አለማቀፍ አመታዊ የማህፀን በር ጫፍ ካንሰር ወር

አለማቀፍ አመታዊ የማህፀን በር ጫፍ ካንሰር ወር ምክኒያት በማድረግ በጎንደር ቅርንጫፋችን ከጎንደር ዩኒቨርሲቲ ኦንኮሎጂ ክፍል ጋር በመተባበር ግንዛቤ በመስጠት አሳልፈናል። ቀን 24/05/16

ሰላም ጤና ይስጥልን እንዴት አላችሁ

አለምፍሬ ፒንክ ሀውስ ካንሰር ፋውንዴሽን ከጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ሆስፒታል ኦንኮሎጅ ክፍል በጋራ በመሆን የማህፀን በር ጫፍ ካንሰር ምርመራ ወርን አስመልክቶ ለጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሴት ሰራተኞች በሙሉ እና ጥሪ ለተደረገላቸው ሌሎች እንግዶች የተዘጋጀው የግንዛቤ ማስጨበጫ ቀን አሳልፈናል።

ዶ/ር መኳንንት የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ክሊኒካል ዳይሬክተር፣ የካንሰር ክፍል ዶክተሮች ዶ/ር እዩኤል፣ዶ/ር አማረ የሽጥላ፣ዶ/ር ኤፍሬም እና ከፓቶሎጅ ክፍል ዶ/ር ጥሩ ዘር በተገኙበት ስለ ማህፀን በር ጫፍ ካንሰር ምርመራ የግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርት ሰጥተዋል፣ በመቀጠል በድርጅታችን/ ፒንክ ሀውስ/ የተሰሩ ስራወችን እና በቀጣይ አገልግሎቱን በሰፊው ለመስጠት ፣የሰውን ህይወት ለመታደግ የሁሉም ማህበረሰብ ርብርብ እንደሚያስፈልግ በዝርዝር አቅርበናል።

በመጨረሻም ዶ/ር መኳንንት የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ሆስፒታል ክሊኒካል ዳይሬክተር እንዳሉት በዓለማችን ብሎም በሀገራችን እየተስፋፋ የመጣውን በሽታ ለመቀነስ እና ለማጥፋት፣ የእናቶችን ሞት ለመቀነስ ከጎናችን ሆኖ እየሰራ ለሚገኘው አለምፍሬ ፒንክ ሀውስ ካንሰር ፋውንዴሽን ምስጋናቸውን አቅርበው ከተቻለ በገንዘብ ፣በዓይነት፣ በሙያዊ ድጋፍ ፒንክ ሀውስን ሁሉም ሰራተኛ በተቻለው አቅም መደገፍ እንዳለበት መልዕክት አስተላልፈዋል።

ABCF pinkhouse

AlemFre PinkHouse Cancer Foundation (APCF) is a nonprofit organization dedicated to helping Ethiopian women abroad and at home, who are burdened with financial need to access screening, diagnosis, and treatment for breast cancer. APCF is also devoted to guiding Ethiopian women to optimal health through increased awareness about breast, Cervical, and other cancer and diseases associated with cancer.

https://www.abcfonline.org
Previous
Previous

ቅዳሜ 16 06 2016 ዓ.ም

Next
Next

አለም ፍሬ ፒንከ ሃውስ ካንሰር ፋውዴስን  ሳምታዊ ትምህርታዊ ፕሮግራም አከናወነ