ቅዳሜ ታህሳስ 13 2016 አዲስ አበባ ፒንክሀውስ

ቅዳሜ ታህሳስ 13 2016 አዲስ አበባ ፒንክሀውስ

በፒንክሀውስ ነባር ታካሚዎች ቆይታቸውን/አገልግሎታቸውን ጨርሰው ሲውጡ በተመሳሳይ በየሳምንቱ የተለያዩ በአቅምም በገንዘብም ደከም ያሉ አዳዲስ ታካሚዎች አገልግሎቱን ለማግኝት ቦታውን ይተካሉ፣ እኛም በየሳምንቱ ለሚመጡ አዳዲስ ታካሚዎች መደገም ያለበትን የግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርቶች እና በአዳዲስ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ግንዛቤዎችን እንሰጣለን፣ጥያቄዎችንም እንዲጠይቁ እናደርጋለን።

በዚህኛው ቅዳሜም የድርጅታችን የበጎ ፈቃድ አምባሳደር አቶ እስክንድር ላቀው ፣ የድርጅታችን የስራ ሀላፊዎች እና እንግዶች በተገኙበት እንደተለመደው ከየካ ክ/ከተማ በመጡ አዳዲስ እና ነባር ባለሙያዎች በአካባቢ ንፅህና አጠባበቅ፣ተጓዳኝ በሽታውችን እንዴት መከላከል እንደሚችሉ እና በታካሚዎች በተነሱ ጥያቄዎች ላይ ጥሩ ቅዳሜን አሳልፈናል፣እንደሁልጊዜው ታካሚዎቻችን በየካ ጤና ጣቢያ ደረጃ መሰጠት ያለባቸውን ነፃ አገልግሎቶች እና መድሀኒቶችን እንደሚያገኙ እና ቅድሚያ እንደሚሰጣቸው ባለሙያዎች ገልፀውልናል።የድርጅታችን አምባሳደር የሆኑት አቶ እስክንድር ታካሚዎች በጥንካሬ እና በብርታት ህክምናቸውን ጨርሰው ወደ ቀደመው ህይዎታቸው መመለስ እንዳለባቸው አስገንዝበው ሳምንታዊ የቅዳሜ ውይይታችን በዚህ መልኩ አጠናቀናል።

ቅድመ ምርመራ እና የካንሰር ግንዛቤ ህይዎትን ያድናል'

Early detection and awareness of cancer saves lives!

cancerawarness #pinkhouse www.abcfonline.org

ድጋፍ ለማድረግ: ንግድ ባንክ 1000464499591

በቴሌ ብር መተግበሪያ

አቢሲኒያ ባንክ፡ 18294001

ቡና ባንክ፡4489527000284

ABCF pinkhouse

AlemFre PinkHouse Cancer Foundation (APCF) is a nonprofit organization dedicated to helping Ethiopian women abroad and at home, who are burdened with financial need to access screening, diagnosis, and treatment for breast cancer. APCF is also devoted to guiding Ethiopian women to optimal health through increased awareness about breast, Cervical, and other cancer and diseases associated with cancer.

https://www.abcfonline.org
Previous
Previous

ቅዳሜ ጥር 18 2016 አዲስ አበባ ፒንክሀውስ

Next
Next

አለምፍሬ ፒንክ ሀውስ ካንሰር ፋውንዴሽን ጎንደር ቅርንጫፍ ወርሃዊ ቡና ጠጡ የግንዛቤ ማስጨበጫ ፕሮግራም